በአንድ ደቂቃ አጭር ፊልሙ ዓለም አቀፍ ሽልማትን ያገኘው ሀብታሙ
በአንድ ደቂቃ አጭር ፊልሙ ዓለም አቀፍ ሽልማትን ያገኘው ሀብታሙ
“ስቶፕ ዋር” (ጦርነት ይቁም) በተሰኘ የአንድ ደቂቃ አጭር ፊልም ዓለም አቀፍ ውድድር ላይ ተሳትፎ ያሸነፈው ወጣቱ ሀብታሙ ሰፊው ለፊልም ጥበብ ጥልቅ ፍቅር አለው።
ከአንድ ዓመት በፊትም ከመላው አፍሪካ ከተወጣጡ ከ400 በላይ አመልካቾች ጋር ተወዳድሮ በኬንያ የአንድ ዓመት የፊልም ጥበብ የትምህርት ዕድል አግኝቶ አጠናቋል።
ሀብታሙ ሽልማት ስላገኘበት የአጭር ፊልም ሥራው፣ ለፊልም ጥበብ ስላለው ፍቅር፣ ዘርፉን የበለጠ ለማወቅ ስላደረጋቸውን ጥረቶች እና ወደፊት ምን ለመሥራት እንዳቀደ ልምዱን ለአቻዎቹ አጋርቷል።